ጎበና: ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ሕይወት (1810-1881): [Gobena: A Military and Political Life (1810-1881)]

ጎበና: ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ሕይወት (1810-1881): [Gobena: A Military and Political Life (1810-1881)]

by Dechasa Abebe
ጎበና: ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ሕይወት (1810-1881): [Gobena: A Military and Political Life (1810-1881)]

ጎበና: ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ሕይወት (1810-1881): [Gobena: A Military and Political Life (1810-1881)]

by Dechasa Abebe

Paperback

$29.95 
  • SHIP THIS ITEM
    Qualifies for Free Shipping
  • PICK UP IN STORE
    Check Availability at Nearby Stores

Related collections and offers


Overview

ጎበና ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ሕይወት (1810-1881) - ለዘመናዊት ኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ታላቅ ሚና ስለተጫወቱት የፖለቲካ ሰውና የጦር መሪ የራስ ጎበና ዳጪን የሕይወት ታሪክ የያዘ መጽሐፍ ነው።

በአራት ክፍሎችና በዓሥራ አራት ምዕራፎች ተዋቅሮ ክፍል አንድ ከዋናው የታሪክ ዳሰሳና ትንተና በፊት ታሪካዊውን ዳራ ለመተረክ ይሞክራል። ሁለተኛው ክፍል ደግሞ ጎበና ሊደርስ ከቻለበት የወታደራዊ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ የእውቅና ጣርያ ድረስ ያለፈባቸውን በፈተና የተሞሉ፣ የዚያኑ ያክል በውጤት የታጀቡ የሕይወት ልምዶቹን ለመዳሰስ ጥረት የሚያደርግ ሲሆን፤ ሦስተኛው ከዚሁ ተያያዥ በሆነ መልኩ ጎበና የተጎናጸፈውን እውቅና እንደምን አድርጎ ሀገራዊ ፋይዳ ወደአለው ነገር እንደለወጠ ለማሳየት ይጥራል። ክፍል አራት የጎበና የመጨረሻ ዘመናት ያለ አቻ ወራሽ ሲጠናቀቁ የኦሮሞ ሕዝብ የተጋረጠበትን ከሀገርና ከመንግሥት ባለቤትነት የመንሸራተት ፈተና ለምን እንደተከሠተ ለማመላከት ጥረት ያደርጋል።

በዝርዝር ምዕራፎቹ ስለ ጎበና እስከ አሁን የነበሩትን የተለያዩ እይታዎችና አመለካከቶች፣ ከጎበና መወለድ በፊት በዓሥራ ዘጠነኛው ክፍለዘመን መጀመሪያና በልደቱ ወቅት የጎበና የትውልድ ቦታ በነበረው ሰሜን ሸዋ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሁኔታ፣ በይበልጥ ደግሞ የኦሮሞና ዐማራ ሕዝብ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መስተጋብሮች ጎበናን እንዴት እንደቀረጹት፣ የጎበናን ልደት፣ ልጅነትና ወጣትነት እንዲሁም የሎሌነት፣ የአማችነት እና ደጅ አጋፋሪነት በመጨረሻም የሽፍትነት ጊዜውን፣ የግዛት መስፋፋትና የሰፊውን ኢትዮጵያ ሀገር የመመሠረት ውጥንና ከምኒልክ ጋር መተዋወቁን ይገልጻል።

ጎበና የተለያዩ ሹመቶችን ለምሣሌ የደጃዝማችነትና ከዚያም የራስነት ሹመትና ማዕረግ ላይ እንዴት እንደደረሰና በተለይም የጦር አበጋዝነትን ያክል ትልቅ ሃላፊነት አንዴት እንደወሰደ በተጓዳኝም "የግዛት ማስፋፋትና ሀገር ማቅናት" ስተራቴጂ እንዴት በጋራ እንደተነደፈ፣ በተለያዩ አቅጣጫዎች በተለያዩ መሪዎች እንደተተገበረ ይተርካል። በመጨረሻም ጎበና ብዙዎቹን የቤት ሥራዎቹን ቀድሞ በማጠናቀቁና ሌሎቹን ባለድርሻ አካላት ድንክዬ በማድረጉ በምኒልክ ዙሪያ ባሉ ሰዎች ጉትጎታና ማጉረምረም በመጀመሪያው ስምምነት መሠረት ሳይሆን ውጤቱን በማጠፍ ጎበና ያስገበራቸውን አካባቢዎች ሌሎች እንደ ተሾሙበት፣ የጎበናን ሃይማኖታዊ ክንውንና የአብያተክርስቲያናት ግንባታ እንቅስቃሴ እንዱሁም ቤተሰባዊ ሕይወቱን በተለይም ጋብቻና ልጆች፣ ሞትና አሟሟቱን በተመለከተ ማስረጃ እስከፈቀደ ድረስ ተገልጾ በመዝጊያውም ስለጎበና የተነገረው ነገር ያለውን አንድምታ በጸሐፊው ግንዛቤ ልክ የማሰሪያ ሐሳብ የተሰጠበት መጽሐፍ ነው።


Product Details

ISBN-13: 9781599072234
Publisher: Tsehai Publishers
Publication date: 09/11/2020
Pages: 324
Product dimensions: 6.00(w) x 9.00(h) x 0.73(d)
Language: Amharic

About the Author

ዶ/ር ደቻሳ አበበ በጥቅምት 3፣ 1967 ዓ. ም በሰሜን ሸዋ ሳያደብርና ዋዩ ወረዳ ሳክላ አቦ የገጠር ቀበሌ ተወለደ። የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በደነባ አንደኛ ደረጃ፣ ሁለተኛ ደረጃውን በእነዋሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትሏል። የመጀመሪያ ድግሪውን ከኮተቤ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ በታሪክ መምህርነት በ1991 ዓ. ም፣ የማስተርስ ድግሪውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በታሪክ በ1995 ዓ. ም እና ከኢንድራጋንዲ ዩኒቨርሲቲ በሶሽዮሎጂ በ2001 ዓ. ም ያገኘ ሲሆን በታሪክ የትምህርት ዓይነት ደግሞ የዶክትሬት ድግሪ በ2008 ዓ. ም ከደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርሲቲ ተቀብሏል። ዶ/ር ደቻሳ በጋምቤላ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ፣ በጅማ ዩኒቨርሲቲ እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በታሪክ መምህርነት ያገለገለ ሲሆን አሁን በዚያው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሚገኘው የአፍሪካ ጥናትና ምርምር ማዕከል በመምህርነትና በተመራማሪነት በማገልገል ላይ ይገኛል። በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ በርካታ የጥናት ወረቀቶችን በተለያዩ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በሚገኙ የምርምር ጆርናሎች ላይ አሳትሟል።

Table of Contents

ዕውቅና

መቅድም

ክፍል አንድ፡ የጥናቱ ዳራ

ምዕራፍ አንድ፡ መንደርደሪያ

ምዕራፍ ሁለት፡ ሸዋ በጎበና የልደት ዘመን

ክፍል ሁለት፡ ፈታኝ የዕድገት መሰላል (1810-1870)

ምዕራፍ ሦስት፡ የጎበና የልጅነትና የወጣትነት ዘመን

ምዕራፍ አራት፡ የሽግግር ዓመታት

ምዕራፍ አምስት፡ የጎበና የጦር አበጋዝነት ሹመት

ክፍል ሦስት፡ ወርቃማ ዓመታት (1870-1878)

ምዕራፍ ስድስት፡ የጎበና “የቱለማ ኮንፌደሬሲ” ምሥረታን ማጠናቀቅ

ምዕራፍ ሰባት፡ የጎበና የደቡብ መጫና የከፋ ዘመቻ

ምዕራፍ ስምንት፡ የጎበና የሰሜን መጫና የአንፊሎ ዘመቻ

ምዕራፍ ዘጠኝ፡ የጎበና የአርሲ ዘመቻ

ምዕራፍ አስር፡ የጎበና የ“ዓረብ” ዘመቻ

ምዕራፍ አስራ አንድ፡ የጎበና የጉራጌ ዘመቻ

ክፍል አራት፡ ሲያልቅ አያምር (1878-1881)

ምዕራፍ አስራ ሁለት፡ የታጠፉ የአጋርነት ስምምነቶችና ውጤታቸው

ምዕራፍ አስራ ሦስት፡ ጎበናና ክርስትና

ምዕራፍ አስራ አራት፡ የጎበና ቤተሰባዊ ሕይወት፣ ሞትና አሟሟት

መደምደሚያ

ዋቢ ጽሑፎች

መጠቁም

From the B&N Reads Blog

Customer Reviews